+ ውሻ
ለጅብ የሚጮኸው ጩኸት በደጅ ላይ ያለ ጅብን እንጂ ቤት ውስጥ ምትርመጠመጠው እንቅልፍ እየነሳች; ንብረት
ምታወድመውን አይጥን አያስደነግጣትም:: የውሻ የትግል ጩኸት ለጅብ እንጂ ለአይጥ አይጠቅምም:: ለአይጥ የድመት
እንጂ የውሻ ጩኸት አያስደነግጣትም:: ስለሆነም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ተሰግረው ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች
በአንድ አቅጣጫ ጩኸት ብቻ መፍትሔት አያገኙም:: ለመናፍቃን ተቃውሞ የምንጨኸው ጩኸት; በመቅደሱ ያሉ
ኢ-ክርስቲያናዊ የሆኑ ዘረኞችን አያስደነግጥም:: ጉቦ ለሚቀበሉ; ገንዘብ የሚዘርፉ አገልጋዮችን በመቃወም ብንጮኽ;
ይህ ጩኸት ዘረኞቹንም; የተሐድሶ መናፍቃንንም አያስደነግጥም:: ስለዚህ ለእያንዳንዱ
የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ችግር ተገቢ የሆነ ጩኸት(ድምጽ) በተገቢው ቦታና ሰዓት ማሰማት አለበን:: ሁላችንም
ክርስቶሳውያን ስለእምነታችን ያገባናል:: ለቤተ ክርስቲያን ዘብ ለመቆም ቄስ; ዲ/ን መሆን አይጠበቅብንም:: ንጹሕ
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጅ መሆናችን ይበቃል:: አንተ; እኔ; አንቺ; እናንተ; እናንቺ(ለሴቶች); እነሱም ሁላችንም
ስለ ቤተ ክርስቲያን እኩል ያገባናል:: ደረጃችንና አቅማችንን ያገናዘበ ውግንና አምላከ ቅዱሳን አምላካችን
እግዚአብሔር ለሁላችን ያድለን; አሜን::
No comments:
Post a Comment